የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብሔራዊ መታወቂያ ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ መሆኑን አሳዉቋል፡፡
ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል ነዉ ያለዉ፡፡
ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም ሲል አሳስቧል፡፡
ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦
- የተማሪ ቤተሰብ
- መምህራን
- የትምህርት አመራሮች እንዲሁም
- የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ ቀርቧል።
ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም
