የ40 ሚሊዮን ዶላሩ ፋብሪካ እና የጋና አዲሱ የንግድ ገደብ

Date:

የጋና መንግሥት አዳዲስ የአገር ውስጥ ፋብሪካዎችን ከውጭ ውድድር ለመጠበቅና ኮንትሮባንድን ለመቆጣጠር በየብስ ድንበሮች የሚደረግ የፓስታ ገቢ ምርትን አገደ።

ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ በቅርቡ በ40 ሚሊዮን ዶላር የተገነባውን የኦላም አግሪ የፓስታ ፋብሪካን መርቀው በከፈቱበት ወቅት እንደገለጹት፣ ውሳኔው የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ለማጠናከር ያለመ ነው።

ፋብሪካው በዓመት 40 ሺህ ቶን ፓስታ የማምረት አቅም ያለው ሲሆን፣ ይህም የሀገሪቱን 40 በመቶ ፍላጎት ይሸፍናል ተብሏል።

ከፓስታ በተጨማሪም እንደ የምግብ ዘይት፣ ሩዝ፣ ስኳር እና ጨርቃጨርቅ ያሉ ምርቶች በየብስ እንዳይገቡ ተከልክለው በባህር ወደቦች ብቻ እንዲገቡ ተወስኗል።

የግብርና ምክትል ሚኒስትር ጆን ዱሜሎ በበኩላቸው፣ ከጎረቤት ሀገራት የሚገቡ ህገ-ወጥ ምርቶች የሀገሪቱን ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ እየጎዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ አዲሱ አሰራር የመንግሥትን የገቢ ፍሰት ለማሳደግና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አረጋግጠዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...