የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2017 ዓ.ም 49 አዋጆችን ማጽደቁን አስታወቀ

Date:

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2017 ዓ.ም የስራ ዘመኑ ከቀረቡለት 56 አዋጆች ውስጥ 49 አዋጆችን ማጽደቁ ተገለጸ።

ምክር ቤቱ የስራ ዘመኑን አፈጻጸም አስመልክቶ ባቀረበው የዕቅድ ክንውን ሪፖርት እንዳስታወቀው ካጸደቃቸው 49 አዋጆች ውስጥ 34 አዋጆች ለቋሚ ኮሚቴዎች ተመርቶ ይፋዊ የሕዝብ ውይይት ተደርጎ በሁለተኛ ንባብ ጸድቀዋል ብሏል።

15 አዋጆች ደግሞ የህዝብ ውይይት ሳይደረግባቸው ወደ ሁለተኛ ንባብ ተሸጋግረው መፅደቃቸውን አመላክቷል።

ለምክር ቤቱ ከቀረቡት 56 የሚሆኑ አዋጆች ውስጥ ሰባቱ አለመጽደቃቸውን የጠቆመው ምክር ቤቱ በተጨማሪም ከ2016 የተሸጋገሩ 2 አዋጆችም በተጠናቀቀው የምክር ቤቱ የስራ ዘመን በ2017 ዓ.ም አለመጽደቃቸውን አስታውቋል፤ አዋጆቹ ምን መሆናቸውን አልጠቀሰም።

በአጠቃላይ 9 አዋጆች ወደ 2018 በጀት ዓመት መሻገራቸውን የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ባቀረቡት የምክር ቤቱን የ2017 በጀት ዓመት የተጠቃለለ የዕቅድ ክንውን ሪፖርት ተመላክቷል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በስራ ዘመኑ የአስፈጻሚ ተቋማት ሚኒስትሮች በምክር ቤቱ በአካል በመገኘት የስድስት፣ የዘጠኝ እና 11 ወራት የዕቅድ ክንውን ሪፖርት እንዲያቀርቡና ከአባላትና ከሕዝቡ በተነሡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ ምላሽና ማብራሪያ እንዲሰጡ መደረጉንም አስታውቋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2017 ዓ.ም የስራ ዘመኑ 43 መደበኛ ስብሰባዎችና 3 ልዩ ስብሰባዎች ማካሄዱን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...