የመኾኒ ከተማ ነዋሪዎች  በህወሓት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

Date:

በመቶዎች የሚቆጠሩ የደቡብ ትግራይ መኾኒ ከተማ ነዋሪዎች፣ ዛሬ በሕወሓት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ነዋሪዎቹ ሰልፍ የወጡት፣ ሕወሓት የደቡብ ትግራይ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን አፍርሶ በድጋሚ ለማደራጀት ማቀዱን የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በቅርቡ ለወይን መጽሄት በሠጡት ቃለ ምልልስ መናገራቸውን በመቃወም ነው።

በተቃውሞ ሰልፉ ላይ”የራያ ህዝብ ድምፅ ይከበር፣ የደብረፂዮንን መግለጫ አጥብቀን እንቃወማለን፣ በመስዋዕትነት ስም ህዝብ መማገድ ይቁም” የሚሉ መፈክሮች ተስተጋብተዋል፡፡

ከትናንት ወዲያ በደቡብ ትግራይ የማይጨው ከተማ ነዋሪዎች፣ ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።

(ዋዜማ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...