1.የመድኃኒት አዳኝ ንጥረ ነገር እና ግብዓቶች የማስመጣት ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1062/2025
2.የመድኃኒት ማሸግ እና መለያ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1091/2025
ፀድቀው ይፋ የሆኑት መመረያዎች የሀገር ውስጥ የመድኃኒት አቅርቦትን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድጋሉ ፣የሕዝብ ጤና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ያጠናክራሉ ፣የኢኮኖሚ እድገትን ያበረታታሉ እንዲሁም በጥራት ምርቶች እንደመሚረቱ ያረጋግጣሉ። በአገራዊ የማምረት አቅም ላይ በራስ መተማመንን ለማምጣት እና ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ጥገኝነትን ለመቀነስ ቁልፍ ስትራቴጂ ናቸው።
የሀገር ውስጥ ፋርማሲዩቲካል አምራቾች የሚያጋጥሟቸው ቁልፍ ተግዳሮቶች የፋርማሲዩቲካል አዳኝ ንጥረ ነገር እና ሌሎች አስፈላጊ ግብአቶች ተደራሽነት ውስንነት እንዲሁም የሙሉ አቅም የማምረቻ ሥራዎችን ለመመስረት የሚያስፈልገው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እና ጊዜን ያጠቃልላል።
እነዚህን ተግዳሮቶች ለመፍታትና የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርትን ለመደገፍ ባለሥልጣኑ አሁን ፀድቀው በይፋ የተመዘገቡ ሁለት ቁልፍ መመሪያዎችን አዘጋጅቷል።
የፋርማሲዩቲካል አዳኝ ንጥረ ነገር እና ሌሎች አስፈላጊ ግብአቶች የማስመጣት ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1062/2025 ጥራት ያለው የፋርማሲዩቲካል አዳኝ ንጥረ ነገር እና ሌሎች አስፈላጊ ግብአቶች ለአገር ውስጥ አምራቾች ተደራሽ በማድረግ ዘላቂ ምርትን በማረጋገጥ የጤና ጥበቃ ስርዓትን በማሻሻል የሀገር ውስጥ የፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪነት ያሳድጋል።
የመድኃኒት ማሸግ እና መለያ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1091/2025 መድኃኒቶችን ለማሸግ እና ለመሰየም ስራዎች ለማከናወን አነስተኛ የቁጥጥር መስፈርቶችን ያስቀምጣል። ይህም ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል እንዲሁም የሀገር ውስጥ ምርትን እድገት ያሳድጋል።
እነዚህ መመሪያዎች ሥራቸውን በመደገፍ፣ አዳኝ ንጥረ ነገር እና ሌሎች አስፈላጊ ግብአቶች አቅርቦትን በማሻሻል እና የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርትን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ለነባርም ሆነ ለአዳዲስ የሀገር ውስጥ አምራቾች ጠቃሚ እድሎችን ይፈጥራሉ።
