የማኅበሩ ፕሬዝዳንት በጸጥታ ኃይሎች ታሰሩ

Date:

የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ዮናታን ዳኛው ዛሬ በጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ማኅበሩ አስታውቋል።

ማኅበሩ እንደገለጸው ፕሬዝዳንቱ የታሰሩት የጤና ባለሙያዎች እያነሷቸው ላሉት ጥያቄዎች ድምጽ በመሆናቸው ነው እንጂ በግል ጉዳያቸው አይደለም።

አቶ ዮናታን ከመታሰራቸው በፊት ለባልደረባቸው በስልክ እንደተናገሩና ለምርመራ እንደሚፈለጉ እንደተነገራቸው ማኅበሩ ገልጿል።

ሆኖም ዛሬ ከቤታቸው ተወስደው መታሰራቸውን ቤተሰቦቻቸው አሳውቀዋል።

የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ፕሬዝዳንቱ መታሰራቸው እጅግ እንዳሳሰባቸው በመግለጫው ያሳወቀ ሲሆን በቀጣይ ምን ሊፈጠር እንደሚችልም ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...