“ከፑቲን ጋር ሐሙስ በቱርክ ለመገናኘት ዝግጁ ነኝ”  ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ

Date:

Update

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ከሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቱርክ ኢስታንቡል ተገናኝተው ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ በኤክስ ገጻቸው ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አሳስበዋል።

የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ በጎ ምልክት መሆኑንም ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠቅሰዋል።

ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ሐሙስ ዕለት በቱርክ ኢስታንቡል ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲንን እጠብቃለሁ ብለዋል።

መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...