“ከፑቲን ጋር ሐሙስ በቱርክ ለመገናኘት ዝግጁ ነኝ”  ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ

Date:

Update

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ከሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በቱርክ ኢስታንቡል ተገናኝተው ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ በኤክስ ገጻቸው ሩስያ ለቀጥታ የሰላም ንግግሮች ያቀረበችውን ሀሳብ በደስታ በመቀበል ነገር ግን ድርድር ከመጀመሩ በፊት የተኩስ አቁም መኖር እንዳለበት አሳስበዋል።

የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የቀጥታ ውይይት ለመጀመር ያቀረቡትን ጥሪ በጎ ምልክት መሆኑንም ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ጠቅሰዋል።

ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ሐሙስ ዕለት በቱርክ ኢስታንቡል ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲንን እጠብቃለሁ ብለዋል።

መላው ዓለም ይህን ለረጅም ጊዜ ሲጠብቀው ቆይቷል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ሆኖም ግን ማንኛውንም ግጭት ለማስቆም የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ያለበት የተኩስ አቁም ስምምነት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...