አቶ መለስ ዜናዊ “ተስፋይ የኋላሸት” በሚል የብዕር ስም የፃፉት “ምኹሕኻሕ ዘይፍልየሉ ማዕፆ” መጽሐፍ “መንኳኳት የማይለየው በር” በሚል ርዕስ በአማርኛ ተተርጉሟል። በቅርቡ ለገበያ ይቀርባል። ልቦለድ ነው። ይህ መፅሐፍ የጓድ መለስ የስነፅሁፍ ችሎታ የተደነቀበት፣ “የትግርኛ ቋንቋ ዳኛቸው ወርቁ” የተባሉበት ስራቸው ነው።
ቀደም ባሉት ጊዚያት ለስነፅሁፉ ቀረብ ያሉና ትግርኛ የሚችሉ ብቻ ያነበቡት መፅሐፍ ሲሆን፤ እነሆ አሁን በተስፋየ አድሐኖም ተተርጉሞ ለሰፊው አንባቢ ዝግጁ ሆኗል። በነገራችን ላይ አቶ መለስ “ገነቲና” የሚል ሌላም የመጀመሪያ የልብ ወለድ ስራ አላቸው።
አሌክስ አብርሃ-
