የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት በእስራኤል እና ኢራን ግጭት አስቸኳይ ስብሰባ ሊያካሂድ ነው

Date:

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በእስራኤል እና ኢራን ግጭት ላይ ለመወያየት አርብ፣ ሰኔ 12/ 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ መጥራቱ ተገለጸ።

አስቸኳይ ስብሰባው የተጠራው በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ፓኪስታን እና አልጀሪያ ጥያቄ መሆኑን የቢቢሲ የአሜሪካ አጋር ሲቢኤስ የዜና ወኪል ዘግቧል።

በተባበሩት መንግሠታት የእስራኤል አምባሳደር ዳኒ ዳኖን እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም የእስራኤል ጥቃትን ተከትሎ ኢራን ባቀረበችው ጥያቄ በኒውዮርክ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ድርጅት ተሰብስቦ ነበር።

በዚህም ስብሰባ ላይ እስራኤል የፈጸመችውን ጥቃቶች “አረመኔያዊ” እንዲሁም “ወንጀል” ነው ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢራን ተወካይ ሰኢድ ራቫኒ ወቅሰው ነበር።

የጸጥታው ምክር ቤት የእስራኤልን ድርጊት እንዲያወግዝ እና ተጠያቂ እንዲያደረጋትም ጠይቀዋል።
bbc Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...