የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በእስራኤል እና ኢራን ግጭት ላይ ለመወያየት አርብ፣ ሰኔ 12/ 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ መጥራቱ ተገለጸ።
አስቸኳይ ስብሰባው የተጠራው በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ፓኪስታን እና አልጀሪያ ጥያቄ መሆኑን የቢቢሲ የአሜሪካ አጋር ሲቢኤስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
በተባበሩት መንግሠታት የእስራኤል አምባሳደር ዳኒ ዳኖን እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም የእስራኤል ጥቃትን ተከትሎ ኢራን ባቀረበችው ጥያቄ በኒውዮርክ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ድርጅት ተሰብስቦ ነበር።
በዚህም ስብሰባ ላይ እስራኤል የፈጸመችውን ጥቃቶች “አረመኔያዊ” እንዲሁም “ወንጀል” ነው ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢራን ተወካይ ሰኢድ ራቫኒ ወቅሰው ነበር።
የጸጥታው ምክር ቤት የእስራኤልን ድርጊት እንዲያወግዝ እና ተጠያቂ እንዲያደረጋትም ጠይቀዋል።
bbc Amharic
