ሕዝበ ሙስሊሙ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ጥሪ ተላለፈ

Date:

ሕዝበ ሙስሊሙ ለመጅሊሱ ምርጫ ከነገ ጀምሮ ለ12 ቀናት የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ኮሚቴው ጥሪ አስተላለፈ።

ሕዝበ ሙስሊሙ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (ለመጅሊስ) ምርጫ ለማድረግ፣ ከነገ ጀምሮ በአቅራቢያው በሚገኝ የወረዳው መስጅድ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ጥሪ ማድረጉን ኢፕድ ዘግቧል።

የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር አብዱልዋሲዕ ዩሱፍ ዓሊ እንዳሉት፤ ላለፉት 5 ወራት ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው ቦርዱ፣ በ2017 ዓ.ም ለሚካሄደው የመጅሊስ ምርጫ ዝግጅቱን አጠናቅቋል። በነገው ዕለትም ምዝገባ ይጀምራል ብለዋል።

ምርጫ ቦርዱ ምርጫውን አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ ለማካሄድ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ገልጿል፡፡

በመሆኑም ሕዝበ ሙስሊሙ መታወቂያውን በመያዝ፣ ከነገ ጀምሮ ለ12 ቀናት በየመስጅዱ በሚደረገው የመራጮች ምዝገባ ተመዝግቦ የመራጭነት ካርድ እንዲወስድ ቦርዱ ጥሪ አቅርቧል።

በምዝገባው ሂደት ለሚያጋጥሙ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት በየመስጅዱ የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ መቋቋሙም በመግለጫው መጠቆሙን ኢፕድ በዘገባው አመልክቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...