የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ በዘጠኝ ወራት 5.2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን ሰበሰበ

Date:

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከአባል የፋይናንስ ተቋማት 5.2 ቢሊዮን ብር ዓረቦን መሰብሰቡን አስታወቀ።

የፈንዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ደሳለኝ አምባው እንደገለጹት ይህ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ11.10 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።

ከተሰበሰበው ዓረቦን ውስጥ 2.67 ቢሊዮን ብር (51.3%) ከግል ባንኮች፣ 2.47 ቢሊዮን ብር (47.5%) ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም 59.49 ሚሊዮን ብር (1.2%) ከማይክሮፋይናንስ ተቋማት የተገኘ ነው።

በተጨማሪም ከጠቅላላው የፈንዱ ኢንቨስትመንት ውስጥ 11.17 ቢሊዮን ብር (92.24%) በመንግስት ግምጃ ቤት ሰነድ ላይ ኢንቨስት ተደርጓል።

የገንዘብ መድን ፈንድ ስራውን ከጀመረ ሁለት አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ነው። ዋና አላማው በባንክና በማይክሮፋይናንስ ተቋማት ውስጥ ተቀማጭ ገንዘብ ላስቀመጡ ግለሰቦችና ድርጅቶች የመድን ሽፋን መስጠት ነው።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የምርጫ ካርድ፡ የአገር ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ

ግዮን መጽሔት :- በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዞ ውስጥ ምርጫዎች የሥልጣን...

አደይ ኢትዮጵያ ጓል አስመራ…!!

የቀድሞ ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የስንብት ቃል ለጠቅላይ ሚ/ር ዐብይ...

ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ሁለተኛው ዙር ድርድር ሊደረግ እንደሚችል ተናገሩ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ሁለተኛ ዙር የሰላም ድርድር...

በ”ፊንቴክ” ኢንቨስትመንት በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ጊዜ ተፈቀደለት

ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ እንዲፈቀድለት ባለፈው አርብ በነበረው...