የኃይል ሥርቆት የፈጸሙ 111 ደንበኞች ላይ ክስ ተመሠረተ

Date:



የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሸገር ሪጅን በ8 ወራት ውስጥ አንድ መቶ አስራ አንድ ደንበኞች የኃይል ሥርቆት መፈጸማቸውን ባደረገው ድንገተኛ ምርመራ እና ክትትል ማግኘቱን አስታውቋል።

ሪጅኑ በ196 ሺሕ ደንበኞች ላይ ባደረገው ድንገተኛ ክትትል 13 በስማርት ቆጣሪዎች፣ 69 በቅድመ ነጠላና ባለሦስት ፌዝ ቆጣሪዎች እና በ29 የድህረ-ክፍያ ቆጣሪዎች ላይ ስርቆቱ መፈፀሙን  የሸገር ሪጅን ኢነርጂ ማኔጅመንት ማናጀር አቶ ግርማ ተናግረዋል።

ዘመናዊ ቆጣሪዎች (ስማርት ) ላይ የተደረገው ስርቆት የታወቀው ቆጣሪዎቹ ወደ መረጃ ቋት በሚልኩት መረጃ ነው።የኃይል ስርቆት በፈፀሙ ደንበኞች ላይ ከ 31 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ እንዲከፍሉ በማድረግ ሊባክን የነበረ ከ17 ሚሊየን በላይ ኪዋት ሰዓት ከብክነት ታድገናል ሲሉ ማናጀሩ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም የኃይል ስርቆት ሲፈጽሙ በተገኙ  ደንበኞች ላይ ክስ መመስረቱ ተገልጿል።የኃይል ስርቆት ተግባር ሲፈፅም የተገኘ አካል በሕግ ከመጠየቁም ባለፈ፣ ይጠቀምበት የነበረው አገልግሎት እንደሚቋረጥ፣ ያለአግባብ ለተጠቀመው የፍጆታ ሂሳብ በታሪፉ መሰረት ተሰልቶ ከዳግም ማስቀጠያ ክፍያና ከተጨማሪ ቅጣት ጋር እንዲከፈል  ይደረጋል፡፡

በተጨማሪም የኃይል ስርቆት መፈፀም በወንጀል የሚያስከስ እና እስከ አምስት ዓመት በእስራት የሚያስቀጣ እንዲሁም እስከ 20 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት የሚያስቀጣ ነው ሲሉ አቶ ግርማ ወግበላ ጨምረው መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ዘግቧል።
@ዳጉ_ጆርናል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...