የኃይል አቅርቦትን ለማሻሻል የ4.3 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ተጀመረ

Date:

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች የሚታየውን የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በ27 በመቶ የሚቀንስ የ4.3 ቢሊዮን ብር ግዙፍ የኃይል ማሻሻያ ፕሮጀክት እየተከናወነ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የሚተገበረው ይህ የአዴሌ (ADELE) ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት 36.74 በመቶ አፈፃፀም ላይ ደርሷል።

ሥራው 703 ኪሎ ሜትር የኔትዎርክ መስመር ዝርጋታን፣ የ2 ሺህ አዳዲስ ትራንስፎርመሮችን ተከላ እና የሌሎች 2 ሺህ ነባር ትራንስፎርመሮችን አቅም የማሳደግ ተግባራትን ያካትታል።

በኮንክሪት ምሰሶና በሽፍን ኬብል የሚከናወነው ይህ ግንባታ የትራንስፎርመር መቃጠል አደጋን በእጅጉ የሚቀንስ ሲሆን፣ አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው የኃይል አቅርቦት ለነዋሪዎች ለማድረስ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...