የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

Date:

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ እጥረት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መምጣቱ በአሽከርካሪዎችና በነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና እያሳደረ ይገኛል።

በቅርቡ የተደረገውን የዋጋ ጭማሪ ተከትሎ የተከሰተው የአቅርቦት ማነስ፤ በተለይም በመቀሌ፣ በጅማ፣ በአምቦ እና በባሕር ዳር ከተሞች አሽከርካሪዎችን ለረጅም ሰዓታት የሰልፍ እንግልት ዳርጓቸዋል።

በመቀሌ አንድ የ20 ሊትር ነዳጅ በህገ-ወጥ መንገድ እስከ 8,000 ብር እየተሸጠ መሆኑን የሚገልጹት ተጎጂዎች፣ ሰዓታትን በሰልፍ ቢያሳልፉም ነዳጅ የማግኘት ዕድላቸው አነስተኛ መሆኑን በምሬት ይናገራሉ።

ሁኔታው የሕዝብ ትራንስፖርት እንቅስቃሴን ከማስተጓጎሉም በላይ፣ አሽከርካሪዎች የሥራ ሰዓታቸውን በማደያዎች ሰልፍ ላይ እንዲያባክኑ አስገድዷቸዋል።

ችግሩ በዚህ ከቀጠለ የትራንስፖርት ዘርፉ ክፉኛ ሊጎዳ ይችላል የሚል ስጋት የነገሰ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው አካላት ለአቅርቦት መቆራረጡ አስቸኳይ መፍትሔ እንዲፈልጉ ተጠይቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...