ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዲሲ ዩናይትድ ስታዲየም ኦውዲ ፊልድ የእራት ግብዣ ተደርጎለታል።
የዲሲ ዩናይትድ ክለብ ባለድርሻ የሆኑት አቶ ኢዮብ ማሞ በእራት መርሐ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ቡድኑ እዚህ በመገኘቱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ” ባለፉት ጊዜያት ብዙ ሥራዎች ተሰርተው እዚህ ደርሰናል። አሁን ጨዋታውን ማድረግ ነው የቀረን። ማሸነፍ ይጠበቅብናል።” ያሉት አቶ ኢዮብ መልካም እድል በመመኘት ብሔራዊ ቡድናችን ካሸነፈ ማበረታቻ ሽልማት እንደሚያበረክቱ ቃል ገብተዋል።
የዲሲ ዩናይትድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ጄሰን ሌቪን ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የማስተናገድ እድል በማግኘታቸው እርሳቸውም ሆነ ክለባቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።
