የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርት ሱዳን በረራ ጀመረ

Date:


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርት ሱዳን የበረራ አገልግሎት ዳግም ጀመረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርት ሱዳን የሚያደርገውን በረራ ከጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዳግም ማስጀመሩን አስታወቀ።

አየር መንገዱ ወደ ፖርት ሱዳን ከጥቅምት 5 ቀን  ጀምሮ በቀን አንድ ጊዜ በረራ እንደሚያደርግ ገልጾ በቀጣይ ከጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ግን በረራዎቹን በቀን ወደ ሁለት ጊዜ እንደሚያሳድግ ጠቁሟል።

በሱዳን ጦር ሰራዊት እና በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ (RSF) መካከል ግጭት ከተቀሰቀሰበት ሚያዚያ 2015 ወዲህ የሱዳን መንግሥት ዋና ከተማዋን ካርቱምን በመልቀቅ አገሪቱን ሲያስተዳድር የቆየው በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በምትገኘው ፖርት ሱዳን ከሚገኝ ጊዜያዊ መቀመጫው እንደነበር ይታወሳል።

ይህንንም ተከትሎ አየር መንገዱ ወደ ፖርት ሱዳን ተከታታይ በረራዎችን ሲያደርግ የነበረ ሲሆን ከወራት በፊት በሀገሪቱ እንደገና ባገረሸው ግጭት ሳቢያ ወደ ፖርት ሱዳን ሲያደርግ የነበረውነ በረራ ለማቋረጥ ተገዶ ቆይቷል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...