የኢጣሊያና ኢትዮጵያ የሕዋ ሳይንስ ትብብር ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄደ

Date:

​በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የኢጣሊያ ምርምር ቀንን (GRIM) ምክንያት በማድረግ፣ በኢትዮጵያና በኢጣሊያ መካከል ያለውን የሕዋ ሳይንስ ትብብር የሚያጠናክር ጉባኤ በአዲስ አበባ ትናንት ተካሂዷል።

በታሪካዊው ፖስታ ቤት የፈጠራ ማዕከል (Creative Hub) በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ የሁለቱ አገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የተመራማሪዎች ቡድን እና የቪላ ኢጣሊያ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

​በጉባኤው ላይ የተፈጥሮ አደጋዎችን መከላከል እና የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

የኢጣሊያ አምባሳደር ሴም ፋብሪዚ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ሁለት ሳተላይቶችን ወደ ሕዋ ማምጠቋ በዘርፉ ያላትን ተነሳሽነት ያሳያል።

​ይህ የሁለት ቀናት መርሃ ግብር በASI እና Telespazio የተዘጋጀውን “Looking Beyond” የተሰኘ አውደ ርዕይ ያካተተ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ በ3,000 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኘውን የእንጦጦ የሕዋ ምርምር ማዕከልን በመጎብኘት አጠናቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...