የእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና ከፕሬዚዳንት ታዬ ጋር ተወያዩ

Date:

ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ የገቡት የእስራኤል ፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ፣ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር እንዲሁም ከ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ጋር ፍሬያማ ውይይቶችን አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ፕሬዚዳንቱን ተቀብለው ባደረጉት ውይይት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በጥልቀት መርምረዋል። ውይይቱ በዋናነት በጋራ ፍላጎቶች ላይ ተመስርቶ የሁለቱን ሀገራት ትብብር ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኮረ እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንት ታዬ በበኩላቸው የእስራኤሉን ፕሬዚዳንት በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ምክክር በኢትዮጵያና በእስራኤል መካከል ያለውን ጠንካራና የቆየ ታሪካዊ እንዲሁም ባህላዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር።

በአጠቃላይ የፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ የዛሬው የኢትዮጵያ ጉብኝት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት እና ዘርፈ ብዙ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...