የእናቶችና ሕፃናትን ጤና ለማሻሻል የ282.4 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈረመ

Date:

የጤና ሚኒስቴር ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር በመላ አገሪቱ የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት እና የሕፃናት (RMNCH) ጤና አገልግሎቶችን ለማጠናከር የሚያስችል ታሪካዊ የፋይናንስ ስምምነት ተፈራርሟል።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፤ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ዘላቂ የጤና ፋይናንስን ለመገንባትና የዜጎችን የጤና ውጤት ለማሻሻል ትልቅ እርምጃ ነው።

በዚህ ስምምነት የልማት አጋሮች 171.2 ሚሊዮን ዶላር ቃል የገቡ ሲሆን፣ መንግስትም አገራዊ ቁርጠኝነቱን በማሳየት ቀሪውን ኢንቨስት በማድረግ ጠቅላላ በጀቱን ወደ 282.4 ሚሊዮን ዶላር አሳድጎታል። ይህም ለዘርፉ ከሚያስፈልገው ሀብት 92 በመቶውን የሚሸፍን ነው።

ይህ ስምምነት የዓለም ባንክ፣ ቢልና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን እና ዩኒሴፍን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተሳተፉበት ሲሆን፤ ኢትዮጵያ የ2030 የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥነዋል።

ስምምነቱ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት ረገድ የላቀ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...