በጋሞ ዞን በደረሰ የናዳና የጎርፍ አደጋ የ30 ሰዎች ህይወት አለፈ

Date:

በጋሞ ዞን አስተዳደር ስር በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች፣ በተለይም በደጋማ ስፍራዎች በጣለው ከባድ ዝናብ ሳቢያ በተከሰተ ድንገተኛ የናዳና የጎርፍ አደጋ የ30 ወገኖች ህይወት ማለፉ ተነገረ።

የዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ ይፋ እንዳደረገው፣ ይህ የተፈጥሮ አደጋ በሰው ህይወት ላይ ካደረሰው መሪር ጉዳት በተጨማሪ በንብረትና በአካባቢው ማህበረሰብ መደበኛ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል።

የአስተዳደሩ አካላት በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ፣ ለሟች ቤተሰቦችና ለዞኑ ህዝብ መጽናናትን ተመኝተዋል።

በአሁኑ ወቅት በአደጋው የተጎዱ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም እንዲሁም መሰል ተጨማሪ አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስፈላጊው የክትትልና የድጋፍ ስራ በከፍተኛ ትኩረት እየተከናወነ ይገኛል።

በመሆኑም ህዝባችን ወቅቱን ያገናዘበ ጥንቃቄ በማድረግና ከአደጋ ስጋት ቀጠናዎች በመራቅ ራሱንና ቤተሰቡን ከተፈጥሮ አደጋዎች እንዲጠብቅ ጥብቅ መልዕክት ተላልፏል። ለወገኖቻችንም ነፍስ ይማር እንላለን።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...