የክለቦች ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ዛሬ ይካሄዳል

Date:

የፈረንሳዩ ፒ ኤስ ጂ እና የእንግሊዙ ቼልሲ ምሽት 4 ሠአት ላይ በዓለም የክለቦች ዋንጫ ፍጻሜ ይገናኛሉ፡፡

በፍጻሜው የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ያነሳው ፒ ኤስ ጂ የተሻለ የአሸናፊነት ግምት አግኝቷል።

ከኋላ ጀምሮ በጠንካራ አደረጃጀት የተገነባው የሊዊስ ኤንሪኬው ፒ ኤስ ጅ ተጋጣሚዎቹን በቀላሉ በማሸነፍ ለፍጻሜው ደርሷል።

የኮንፈረንስ ሊጉ አሸናፊ ቼልሲ ተጫዋቾች በዛሬው ጨዋታ ፒ ኤስ ጅ ተገማች ቢሆንም ለሁሉም መፍትሄ አለን እያሉ ነው።

ተጫዋቾቹ ፒ ኤስ ጅን ማሸነፍ የምንችለው እኛ ብቻ ነን ብለዋል።

በምሽቱ ጨዋታ ጠንካራ ተጋጣሚዎችን ተራ የሚያስመስለው የኤንሪኬ የጨዋታ እሳቤና የማሬስካ ልጆች ምላሽ ይጠበቃል።

አሰልጣኝ ኤንሪኬ ሰነፍ እየተባለ የሚታማውን ባለ ተሰጥኦ ደምበሌን ወደ አስፈሪ እና ውጤታማ ተጫዋችነት የቀየሩበትና ቡድኑን ያዋቀሩበት መንገድ ከበርካቶች አድናቆት አስችሯቸዋል።

ለፍጹምነት የቀረበ የመሰለው የእርሳቸው ፒ ኤስ ጅም በዘንድሮው የውድድር ዓመት የተሳተፈባቸውን ዋንጫዎች ጠራርጎ ወስዷል።

በርካታ ተጫዋቾችን ያዘዋወረው ቼልሲም በማሬስካ ስር መሻሻሎችን ያሳየ ሲሆን በአይደክሜው ካይሴዶና ኤንዞ ፈርናንዴዝ የተገነባው አማካይ በርካታ ቦታዎችን የሚያካልል እና ጠንካራው ክፍል ነው።

በተጨማሪም እንደ ኮል ፓልመር ያሉ ልዩነት ፈጣሪ ተጫዋቾች በምሽቱ ጨዋታ የሚኖራቸው ሚናም ተጠባቂ ነው።

በፍጻሜ ጨዋታው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደሚገኙ በትናንትናው ዕለት መገለጹ ይታወሳል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...