ድርጅቱ በበሽታው የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር መጨመርን ተከትሎ ለአራተኛ ጊዜ የአስቸኳይ ኮሚቴ ስብሰባ ሲያደርግ የድርጅቱ ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በበሽታው የሚያዙ ሰዎች መጨመር የዓለም አቀፍ የህብረተሰብ የጤና ስጋት መስፈርትን ያሟላል ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በሽታው በተለይ በምዕራብ አፍሪካ በእጅጉ እየተስፋፋ መሆኑን በመግለፅ ከአፍሪካ ውጪ ወደ ሌሎች አህጉራትም መዛመት መጀመሩን አንስተዋል።
ድርጅቱ፥ የድጋፍ ማነስ በሽታውን ለመቆጣጠር ፈተና እንደሆነበትና ዓለም አቀፍ ምላሽ እንደሚያስፈልግም ገልጿል።
በአፍሪካ በዝንጀሮ ፈንጣጣ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ17 ሺ ያለፈ ሲሆን ዲሞክራቲክ ኮንጎ ከፍተኛውን ቁጥር ትይዛለች።
በበሽታው ባለፈው ሳምንት ከተመዘገቡት ተጠቂዎች ውስጥ 53 በመቶዎቹ ከሴራሊዮን ናቸው ተብሏል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ግንቦት 17 ቀን 2025 ዓ.ም በበሽታው የተያዘ ሰው በሞያሌ አከባቢ መገኘቱ ይፋ ከሆነ በኋላ ያለፈ የመጀመሪያ ሰው ማስመዝገቧ ይታወሳል።
እስከ ሰኔ 2 ድረስ ባለው ጊዜም 84 የላብራቶሪ ምርመራዎቾን በማድረግ 18 ሰዎች መያዛቸውንና የአንድ ሰው ህይወት ማለፉ ተገልጿል።
@TikvahEthMagazine
