የግድያ ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ በ16 እና በ15 ዓመት ጽኑ እሥራት ተቀጡ 

Date:


የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ
ቡድን ተጫዋች አለልኝ አዘነ ግድያ «ጥፋተኛ»’ ያላቸውን ሁለት ግለሰቦች በ16 እና 15 ዓመት ጽኑ እሥራት ቀጣ።

ፍርድ ቤቱ በተከሳሾቹላይ ቅጣቱን የወሰነው ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ በዋለው ችሎት ነው። ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን ሊጥል የቻለው ተካሳሾቹ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት የ26 ዓመት ወጣት የሆነውን አለልኝ አዘነን አርባ ምንጭ ከተማ ውስጥ በመግደልና ራሱን ያጠፋ እንዲመስል በማድረግየግድያ ወንጀል በመፈፀማቸው ነው ተብሏል።


በወንጀሉ የተጠረጠሩ 1ኛ ተከሳሽና የሟች አለልኝ አዘነ ባለቤት ወ/ሮ
አደይ ጌታቸውን እና 2ኛ ተከሳሽ ሉንጎ ሉቃስን በፍርድ ችሎት ሲያከራክር መቆየቱን ለዶቼ ቬለ የገለጹት የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያኃላፊ አቶ ጤናው ጨርቆስ «የተከሳሾቹ ድርጊት በሰውና በሠነድ ማስረጃዎች በመረጋገጡ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት የቅጣት ውሳኔ አሳልፏል።

በውሳኔው መሠረትም 1ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ አደይ ጌታቸው ላይ የ16 ዓመት እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽ ሉንጎ ሉቃስላይ 15 ዓመት ፅኑ እስራት የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል» ብለዋል።


መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም አርባ ምንጭ ከተማ ውስጥ በሰው እጅ ሕይወቱ አልፏል የተባለው አለልኝ አዘነ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን እና ለባሕር ዳር ከነማ ተሰልፎ በመጫወት እንደሚታወቅ ከሀዋሳሸዋንግዛው ወጋየሁ የላከልን ዜና ያመለክታል።


DW Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...