የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ከጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ ጋር

Date:

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ጋር ዛሬ ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም. በስልክ መነጋገራቸውን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ዛሬ ባደረጉት የስልክ ውይይትየመረጋጋት እና የኢትዮጵያ የኤኮኖሚ እድገት እንዲሁም የአፍሪቃው ቀንድን በተመለከተ ሁለቱ ሃገራት በሚጋሯቸው ግቦች ላይ ማተኮራቸውን አመልክቷል።

በዚህ ውይይትም የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሪቢዮ ውይይት እና አካባቢያዊ መረጋጋት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት መስጠታቸውም ተጠቅሷል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረገጹ ባወጣው መረጃ ማርኮ ሩቢዮ የኢትዮጵያን የኤኮኖሚ ማሻሻያዎች ማድነቃቸውን በማመልከት፤ ለአሜሪካ የንግድ እና የመዋዕለንዋይ ፍሰት አማራጭ የመሆን አቅም ለመኖሩ አጽንኦት መስጠታቸውንም አክሎ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...