የጭነት መኪና ተገልብጦ የ11 ሰዎች ህይወት አለፈ

Date:

በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ሸነን ዱጎ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 11 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የዞኑ ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

በተለምዶ አይሱዙ የተሰኘው የደረቅ ጭነት መኩና 42 ሰዎችን ከተለያዩ ሸቀጦች ጋር ጭኖ ከዋልዳያ ከተማ ወደ መሰላ ወረዳ በመጓዝ ላይ ሳለ በትላንትናው ዕለት ምሸት 2:30 ላይ ነው አደጋው የደረሰው።

መኪናው 42 ሰዎዎችን ከተለያዩ እቃዎች ጋር አብሮ ጭኖ የነበረ ሲሆን መስመሩን በመሳት ከ50 እስከ 70 ሜትር በሚርቅ ገደል ውስጥ የገባ ሲሆን በዚህም የ 11 ሰዎች ህይወት ማለፉ ነው የተገለጸው።

በአደጋው በተጨማሪም በ28 ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን በሂርና የመጀመሪያ ሆስፒታል እንዲሁም በጭሮ አጠቃላይ ሆስፒታል ክትትል እየተደረገላቸው ነው።

የአደጋው ምክንያትም የጥንቃቄ ጉድለትና ከአቅም በላይ መጫን መሆኑን የወረዳው የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኃላፊ ኢንስፔክተር ረቢራ አየለ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...