የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ትርክቶች የያዘ መጽሐፍ ታተመ

Date:

•  መጽሐፉን ያሳተሙት ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ ሚቸል ኮሎን ናቸው

የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ትርክቶች የያዘ፣ “የእኔ ተጋድሎ ለኤርትራ እና ለአፍሪካ” የሚል ርዕስ ያለው አዲስ መጽሃፍ በእንግሊዝኛ ታትሟል።

ከኢሳያስ ጋር በአገራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያደረጓቸውን ተከታታይ ቃለ ምልልሶች ቃል በቃል በማሰባሰብ በፕሬዚዳንቱ ፍቃድ ያሳተሙት፣ ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ ሚቸል ኮሎን ናቸው።

መጽሃፉ የኤርትራን “ራስን የመቻል” መርህና ኢሳያስ ስለ ዓለማቀፉ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ሥርዓት ያላቸውን አመለካከት ለአፍሪካዊያን ወጣቶች ለማስተዋወቅ የታለመ ሲኾን፣ በአማርኛና ሌሎች ቋንቋዎችም ይታተማል ተብሏል።

መጽሃፉ ካካተታቸው ምዕራፎች መካከል፣ “ኤርትራና ቅኝ ግዛት”፣ “የሱዳንና አፍሪካ መከፋፈል”፣ “ኤርትራ ከአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም የገጠማት ጣልቃ ገብነት”፣ “የአሁኗ ኤርትራ ተግዳሮቶች” እና “ፕሮፓጋንዳን እንዴት መቋቋም ይቻላል?” የሚሉ ይገኙበታል። ኢትዮጵያዊው የታሪክ ተመራማሪ፣ ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የመጽሐፉን ማጠቃለያ ጽፏል፡፡

(ዋዜማ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...