ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ሩሲያ በኢትዮጵያ ኢንቨስት የምታደርግባቸውን ዘርፎች እንድታሰፋ ጥሪ አቀረቡ

Date:



የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንታዊ ሥራ አስፈፃሚ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ማክሲም ኦሬሽኪን እና ከሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭን ጋር ተገናኝተው በስትራቴጂካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

“ሩሲያ በተለያዩ የትብብር ዘርፎች ለኢትዮጵያ ለምታደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድናቆት አለን፡፡ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ እና በማዕድን ልማት እንዲሁም በማዳበሪያ ምርት፣ በብረታ ብረት ኢንዱስትሪ እና የኒውክሌር እና ታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶችን ጨምሮ በኃይል መሠረተ ልማት፤ ለሩሲያ ኢንቨስትመንት እና የጋራ ትብብር ጥሪ እናቀርባለን” ብለዋል፡፡  

▫️ እነዚህ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች በዘላቂ ልማት፣ በቀጣናዊ ደህንነት እና በጋራ ብልጽግና ላይ በማተኮር የኢትዮጵያ-ሩሲያ አጋርነትን ወደ አዲስ የስትራቴጂካዊ ትብብር ደረጃ ለማሳደግ ማሳያ ናቸው ሲል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማህበራዊ ገጹ አስታውቋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...