«ግብጽ ዛቻውን አቁማ ወደ ድርድር ትግባ!»

Date:

ታዋቂው የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝ ዶ/ር ዴቪድ ማትሳንጋ ግብጽ በኢትዮጵያ የውሃ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ የምታሳየውን ኃይለኛ ተቃውሞና ዛቻ አጥብቀው አወገዙ።

ግብጽ የናይልን ጉዳይ እንደ ፖለቲካ መሣሪያ እየተጠቀመችበት መሆኑን የገለጹት ተንታኙ፣ ሀገሪቱ ዛቻውን በመተው ስጋቶቿን ይዛ ወደ ድርድር ጠረጴዛ መምጣት እንዳለባት አሳስበዋል።

ኢትዮጵያ ፋብሪካዎችን ለማንቀሳቀስ እና የኢኮኖሚ እድገቷን ለማፋጠን ኤሌክትሪክ እንደሚያስፈልጋት የገለጹት ዶ/ር ማትሳንጋ፣ ወንዞቿ ወደ ውጭ ስለሚፈሱ ብቻ ልማቷን ልታቆም እንደማይገባ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ዓላማ ጎረቤት ሀገራትን መጎዳት ሳይሆን የውሃ ሀብቷን በፍትሃዊነት መጠቀም መሆኑንም ገልጸዋል።

በመጨረሻም ግብጽ ወታደራዊ ዛቻዎችን እና የጦርነት ንግግሮችን እንድታቆም አሳስበዋል። ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከመውሰድ ይልቅ፣ ሁለቱ ሀገራት ወደ አፍሪካ ህብረት በመመለስ በውይይት እንዲፈቱት ጥሪ አቅርበዋል።

FMC English

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...

በብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከ710 ሚሊዮን ዶላር በላይ ፍላጎት የቀረበበት መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የ500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ የውጭ...