ጣሊያን ለኢትዮጵያ የቡና ዘርፍ 10 ሚሊዮን ዩሮ ብድር አጸደቀች

Date:

የጣሊያን መንግስት የኢትዮጵያን የቡና ጥራትና ምርት ለማሳደግ 10 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ማፅደቁ ተነግሯል።

ብድሩ የኢትዮጵያን ቡና አምራቾች፣ አቅራቢዎችንና ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላትን ይረዳል መባሉን ካፒታል ለመረጃው ለመረዳት ችሏል።

ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው ፕሪሚየም ጥራት ያለው ቡና ለማምረት እና የኤክስፖርት ገቢን ለማሳደግ የ15 ዓመት ስትራቴጂ እየተገበረች ቢሆንም በዘርፉ ካሉት ዋና ዋና ተግዳሮቶች መካከል አንዱ የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነት እንደሆነ ተጠቁሟል ።

ኢትዮጵያ ባለፈው በጀት ዓመት ብቻ በቡና የወጪ ንግድ 1.43 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘች ሲሆን በዚህ በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 8 ወራት ውስጥ 157,000 ሜትሪክ ቶን ቡና በመላክ 1.3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ታዉቋል።CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...