ፊፋ የኢራንን ጥያቄ ውድቅ አደረገ

Date:

ይህ ጥያቄ የቀረበው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቡድኑን ደህንነት በተመለከተ በሰጡት አስተያየት እና በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለው ውጥረት በመጨመሩ ምክንያት የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጨዋታዎቹ ወደ ሜክሲኮ እንዲዛወሩ በመጠየቁ ነው።

ፊፋ ባወጣው መግለጫ ሁሉም ተሳታፊ ሃገራት አስቀድሞ በወጣው የጨዋታ መርሃ ግብር መሰረት በተመደቡባቸው ከተሞች ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ በማሳወቅ ኢራን በአሜሪካ የምታደርጋቸው ጨዋታዎች እንደማይቀየሩ አረጋግጧል።

ኢራን በምድብ ጨዋታዎቿ ሰኔ 9 ቀን (June 15, 2026) ከኒውዚላንድ እንዲሁም ሰኔ 15 ቀን (June 21, 2026) ከቤልጂየም ጋር በሎስ አንጀለስ የምትጫወት ሲሆን የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዋን ሰኔ 20 ቀን (June 26, 2026) በሴያትል ከግብፅ ጋር ለማድረግ ተመድባለች።

ምንም እንኳን የኢራን ስፖርት ሚኒስቴር ከውድድሩ የመውጣት ፍንጭ ቢሰጡም የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የእስያ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ግን ቡድኑ አሁንም በውድድሩ ላይ እንደሚሳተፍ ገልጸዋል። ኢራን ከውድድሩ የምትወጣ ከሆነ በእርሷ ምትክ ለመሳተፍ እንደ ኢራቅ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ያሉ ሃገራት ከፍተኛ እድል እንዳላቸው ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...