ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ የትግራይን ማዕድናት እየተበዘበዘ ነዉ አሉ

Date:

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ፣ የውጭ አካላት የትግራይን ማዕድናት እየበዘበዙ ይገኛሉ በማለት ዛሬ መቀሌ ውስጥ በዘርፉ ዙሪያ በተካሄደ መድረክ ላይ መናገራቸውን የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ኾኖም ጀኔራል ታደሠ “የውጭ አካላት” ያሏቸውን ማዕድን መዝባሪዎች ማንነት ለይተው እንዳልጠቀሱ ተነግሯል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ የማዕድናት ምዝበራን ለመከላከል ያቋቋመው ግብረ ኃይል፣ ከሰሜን ምዕራብ ዞን ብቻ 440 የወርቅ ማውጫ ማሺኖችን ከሕገወጥ የማዕድን ቦታዎች መያዙን በመድረኩ ላይ ባቀረበው ሪፖርት መናገሩን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

ትግራይ በተያዘው ዓመት ከወርቅ ማዕድን አውጪዎች 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ትጠብቅ እንደነበር የጠቀሰው ግብረ ሃይሉ፣ በዓመቱ የተገኘው ግን 24 ሚሊዮን ብር ብቻ እንደሆነ ገልጧል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...