ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል የሚያጭበረብሩ ግለሰቦች መኖራቸውን የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ

Date:


የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት እንዳስታወቀው አንዳንድ ህገወጦች በምስሉ ላይ የሚታየውን የአየር መንገድውክልና እና መሰል ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል ህብረተሰቡን በማጭበርበር የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት እየሞከሩ መሆኑን ለተቋሙ በደረሰው ጥቆማ መረዳት መቻሉን አስታውቋል።

ተቋሙ እንዲህ አይነቱን የወንጀል ድርጊት እንደማይታገስ እና ተከታትሎ ለህግ እንደሚያቀርብ ያስታወቀ ሲሆን ህብረተሰቡም በእንደዚህ አይነት ሃሰተኛ ሰነድ እንዳይጭበረበርና መሰል አጠራጣሪ ሁኔታ ሲኖር ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎች በህግ ተጠያቂ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት የሚመነጩ የውክልና ሰነዶች ባር ኮድ ያላቸው ሲሆኑ ልዩ ውክልና ከሆነ ደግሞ የራሱ የሆነ መለያ ( security feature) እና ኤሌክትሮኒክስ/ደረቅ ማህተም የያዙ በመሆኑ በቀላሉ በሃሰተኛ መንገድ ሊዘጋጁ የማይችሉ መሆናቸውንም ተቋሙ አረጋግጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን...

‹‹ሃገረ ትግራይ›› በዘመናት መነፅር ሲታይ

(አጭርዳሰሳ) በወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ) የመጽሐፉርዕስ፡- ሃገረ ትግራይ የመጽሐፉ ዓይነት፡-...

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...