ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል የሚያጭበረብሩ ግለሰቦች መኖራቸውን የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ

Date:


የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት እንዳስታወቀው አንዳንድ ህገወጦች በምስሉ ላይ የሚታየውን የአየር መንገድውክልና እና መሰል ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል ህብረተሰቡን በማጭበርበር የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት እየሞከሩ መሆኑን ለተቋሙ በደረሰው ጥቆማ መረዳት መቻሉን አስታውቋል።

ተቋሙ እንዲህ አይነቱን የወንጀል ድርጊት እንደማይታገስ እና ተከታትሎ ለህግ እንደሚያቀርብ ያስታወቀ ሲሆን ህብረተሰቡም በእንደዚህ አይነት ሃሰተኛ ሰነድ እንዳይጭበረበርና መሰል አጠራጣሪ ሁኔታ ሲኖር ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎች በህግ ተጠያቂ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት የሚመነጩ የውክልና ሰነዶች ባር ኮድ ያላቸው ሲሆኑ ልዩ ውክልና ከሆነ ደግሞ የራሱ የሆነ መለያ ( security feature) እና ኤሌክትሮኒክስ/ደረቅ ማህተም የያዙ በመሆኑ በቀላሉ በሃሰተኛ መንገድ ሊዘጋጁ የማይችሉ መሆናቸውንም ተቋሙ አረጋግጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...