በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ የማቋቋም መርሃ ግብር ዳግም መጀመሩን የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስታውቋል።
የተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና የሀገራት ተወካዮች በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ የማቋቋም ትግበራ ሂደት ተመልክተዋል።
የአፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአውሮፖ ኅብረትና የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች በመቐለ የተሃድሶ ማዕከል በመገኘት የስራውን ሂደት ምልከታ አድርገዋል።
