ለማህበረሰቡ በነፃ የሚሰጡ መድሀኒቶች በግል የጤና ተቋማት ውስጥ ሲሸጡ ተገኝ

Date:

በጤና ተቋማት ላይ በየአመቱ በሚደረግ ቁጥጥር ብዙ ግኝቶች መኖራቸውን የገለፁት በጤና ሚኒስቴር የጤናና ጤና ነክ ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ እንዳልካቸው ፀዳል ናቸው።

ከእነዚህም ውስጥ አንደኛውም በመንግስት በጀት ተገዝተውና ለማህበረሰቡ በነፃ የሚሰጡ መድሀኒቶችን ከመንግስት ተቀማት ወጥተው ሲሸጡ መገኘታቸውን እንደሆነም ተናግረዋል።

እነዚህ ተቋማት ላይም አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው አንስተው በተመሳሳይም በመደበኛ አሰራር ለታካሚዎች የሚውሉ መድሀኒቶች በህገወጥ መንገድ እንደሚወጡም ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በቁጥጥር ወቅት በየደረጃው በቂ የሆነ እውቀትና ችሎታ እንዲሁም የህክምና መሳሪያ ሳይኖር ነገር ግን ከአቅም በላይ የሚሰሩ ተቋማት መገኘታቸውን አንስተዋል፡፡

የንፅህና አያያዝ ስርዓቱ ላይም ከፍተኛ ችግር የታየባቸው መገኘታቸውን አንስተው ይህም በአጠቃላይ የታካሚ ደህንነት ችግር ውስጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመሆኑም አጠቃላይ በመድሀኒት አቅርቦትና ዙሪያ ያለውን ችግር ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚሰራው ስራ በስፋት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ስራ አስፈፃሚው አስታውቀዋል።

አሐዱ ራድዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ንባብ ለህይወት!” ታላቅ የንባብ ሳምንት እና የመጻሕፍት አውደ ርዕይ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እና የንባብ ለህይወት...

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...