ለሰባት ቀናት ምህላ ታወጀ

Date:

በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት በተለይ በቆላማ ወረዳዎች ክረምቱ ወቅቱን ጠብቆ ባለመግባቱና የዝናብ እጥረት በመከሰቱ ጸሎተ ምኅላ ታውጇል።

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ኹሉም ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተክርስቲያን ከዛሬ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ7 ቀናት የሚቆይ ምኅላ አውጀዋል።

ኹሉም ሕዝበ ክርስቲያን በየአብያተ ክርስቲያናቱ ዘወትር ጠዋት በመገኘት በተሰበረ ልብ ወደ እግዚአብሔር እንድጸልይ ብፁዕነታቸው ትናንት ሐምሌ 19 ቀን 2017 ዓ.ም አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። 

ትናንት አዳሩን በወልዲያ መጠነኛ ዝናብ ቢዘንብም በቆላማው ቀበሌዎች፣ በቆቦ፣በአላማጣ እንዲሁም በራያ አዘቦ እስካሁን ዝናብ እንዳልዘነበ ተሰምቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...