የተቃጠለዉ ‎‎ሆስፒታሉ በቀን 700 ታካሚዎች አገልግሎት የሚያገኙበት ነበር

Date:



‎በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተከሰተው የእሳት አደጋ በሰዎች ጉዳት ባያደርስም በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

‎የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጉቼ ጉሌ (ዶ/ር)፣ “በርካታ ታካሚዎች የተኙባቸው ክፍሎች ስለነበሩ ሠራተኞች በሙሉ ታካሚ ማውጣት ላይ ትኩረት ስላደረጉ በውስጥ የነበሩ በርካታ ንብረቶች ተቃጥለው ወድመዋል” ሲሉ ተናግረዋል።

‎ሆስፒታሉ በቀን 700 ታካሚዎች አገልግሎት የሚያገኝበት መሆኑን ተገልጿል።‎በመሆኑንም ሆስፒታሉ ወደ ነበረበት እንዲመለስና አገልግሎት እንዲሰጥ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ አጋራ ድርጅቶች አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጥሪ አቅርበዋል።

‎ከጤና ሚኒስቴር የተወጣጣ ቡድን ዛሬ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ያደረሰውን ጉዳት በቦታዉ በመገኘት የተመለከተ ሲሆን የጤና ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ ሆስፒታሉን በአጭር ጊዜ አገልግሎት ለማስጀመር ጤና ሚኒስቴር ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን አስፈላጊዉን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ፣ የወላይታ አስተዳዳሪ፣ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር፣ የጋሞ ዞን  ‎አና ለሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...