ለቀድሞዋ ርዕሰ ብሔር ሳህለወርቅ ዘውዴ የምስጋና መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው

Date:

የምስጋና ፕሮግራሙን ያዘጋጁት በበጎ ፍቃድ የተሰባሰቡ ሴቶችና በሴቶች የሚመሩ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መሆናቸውን ሰምተናል።

ዝግጁቱም ፕሬዝዳንቷ በስራ ዘመናቸው ላከናወኗቸው ስራዎች ምስጋና ለማቅርብ ያለመ መሆኑ ተነግሯል።

የመጀመሪያዋ የኢፌዴሪ ሴት ፕሬዚዳንት የነበሩት ሳህለወርቅ ዘውዴ በፕሬዚዳንትነት ዘመናቸውና በዲፕሎማትነታቸው የሴቶችን አመራር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ፣ የፆታ እኩልነት ለማስፈን እና ሴቶችን በሁሉም ዘርፍ ለማብቃት ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸው በዝግጅቱ ላይ ሲነገርላቸው ሰምተናል።

በተለይ በርካት ወጣት ሴቶች ወደ ሀላፊነት እንዲመጡ አስችሏል የተባለው ፕሬዚዴንሻል ኢኒሼቲቭ ፕሮግራም አበርክቶው የጎላ ሆኖ ሲጠቀስላቸው ሰምተናል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የቀድሞዋን ፕሬዝዳንት የህይወት ታሪክ የተመለከተና በመቅዲ ፕሮዳክሽን የተዘጋጀ አጭር ዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል።

ከዚህ በተጨማሪም የቀድሞዋን ፕሬዚዳንት እና ዲፕሎማት ሳህለወርቅ ዘውዴን በስራ አጋጣሚ የሚያውቋቸው አምሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ፣ ብሌን ወርቁ፣ ወ/ሮ ኢትዮጵያ ጥላሁን፣ ስኂን ተፈራ፣ ወ/ሮ ፅጌ ኃይሌ እና ሌሎች ምስክርነት ሰጥተዋል።

በሸራተን አዲስ በተካሄደው ዝግጅቱ ላይ አብረዋቸው የሰሩ ሰዎች ፣ የሴት ማሀበራት ተወካዮች ፣ ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል።

በ1942 በአዲስ አበባ ተወልደው ያደጉት የቀድሞዋ ረዕሰ ብሔር ሳህለወርቅ ዘውዴ በጅቡቲ፣ በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ተወካይ ሆነው ሰርተዋል።

በኬንያ የተባበሩት መንግሥታት ዳይሬክተር ጄነራል ሆነው መስራታቸውም ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...