ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ተሾመለት

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ሆነው ለተሾሙት አቶ ባረክ ታደሰ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሸዊት ሻንካ የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የኢትዮጵያውያን ቤት እንድሆን እንሰራለን፤ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የተሻለ ውጤት እንድመዘገብ የአሰራር መመሪያዎችንና ደንቦችን ተከትሎ የሚተገብርና የሚያስተገብር አመራር መኖር ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ዘርፉን ወደ ተፈለገው ደረጃ ከፍ ለማድረግም ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ባረክ ታደሰ ትልቅ አቅም በመሆናቸው እንኳን ደህና መጡ ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት አቶ ባረክ ታደሰ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ልባዊ ምስጋና በማቅረብ ሀገራችን በኪነጥበቡ ዘርፍ ተጠቃሚ እንድትሆን ሁሉን ያማከለ ኪናዊ ስራዎችን ከታችኛው አደረጃጀት ጀምሮ በጋራ መስራትን ይጠይቃል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ የተሰጠኝን ሃላፊነት በአግባቡ ለመወጣትም አቅጣጫ ሰጭ ከፍተኛ አመራሮች ከጉኔ በመኖራቸው እድለኛ ነኝ ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...