ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ተሾመለት

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ሆነው ለተሾሙት አቶ ባረክ ታደሰ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሸዊት ሻንካ የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የኢትዮጵያውያን ቤት እንድሆን እንሰራለን፤ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የተሻለ ውጤት እንድመዘገብ የአሰራር መመሪያዎችንና ደንቦችን ተከትሎ የሚተገብርና የሚያስተገብር አመራር መኖር ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ዘርፉን ወደ ተፈለገው ደረጃ ከፍ ለማድረግም ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ባረክ ታደሰ ትልቅ አቅም በመሆናቸው እንኳን ደህና መጡ ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት አቶ ባረክ ታደሰ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ልባዊ ምስጋና በማቅረብ ሀገራችን በኪነጥበቡ ዘርፍ ተጠቃሚ እንድትሆን ሁሉን ያማከለ ኪናዊ ስራዎችን ከታችኛው አደረጃጀት ጀምሮ በጋራ መስራትን ይጠይቃል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ የተሰጠኝን ሃላፊነት በአግባቡ ለመወጣትም አቅጣጫ ሰጭ ከፍተኛ አመራሮች ከጉኔ በመኖራቸው እድለኛ ነኝ ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...