ለክልል ደም ባንኮችን ድጋፍ ማድረጉን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ

Date:

ከዓለም ባንክ በተገኘ ድጋፍ 100 የፕላዝማ ፍሪጆች እና አንድ ሺህ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ደም መለገሻ አልጋዎች ለክልላዊ ደም ባንኮች መሰጠታቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ይህ ድጋፍ የደም አቅርቦትን በማሻሻል በተለይ የእናቶችና ህጻናት ሞትን ለመቀነስ የሚያስችል መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ገልጸዋል።

ዶ/ር መቅደስ የደም ባንክ አገልግሎት ከሌሎች በላይ ጥንቃቄን እንደሚፈልግ አስታውሰው፣ ይህ ድጋፍ አገልግሎቱን በጥራት፣ በተደራሽነትና በፍትሃዊነት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን አክለዋል።

በቀጣይም የደምና ህብረ-ህዋስ አገልግሎትን በሃገር አቀፍ ደረጃ ለማጠናከር እና የክልል ደም ባንኮችን አቅም ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ደምና ህብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት ዋና ዳይሬተር ዶ/ር አሸናፊ ታዘበው በበኩላቸው፣ ድጋፉ የክልል ደም ባንኮች የግብአት እጥረትን በመቅረፍ ዘላቂ፣ ውጤታማና ደህንነቱ የተጠበቀ የደም አሰባሰብና አቅርቦት ስርአት እንዲኖራቸው አስተዋጾ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም፣ በድጋፍ የተሰጡት ቁሳቁሶች የደም ግብአትን ለማሻሻል የሚረዱ በመሆናቸው በአግባቡ አገልግሎት ላይ መዋል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...