ሕገ-ወጥ የፋይዳ መታወቂያን በሚያትሙ አካላት ላይ እርምጃ ለመውሰድ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገለጸ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ ትክክለኛ ያልሆነ ሕገ-ወጥ የፋይዳ መታወቂያን በማተም ለግለሰቦች በሚሰጡ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።

የጽ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ዮዳሄ አርያስላሴ ለአሐዱ እንደገለጹት፤ ‘የፋይዳ መታወቂያን በአጭር ጊዜ እንጨርስላችኋለን’ በማለትና በአሰራሩ መሠረት መመዝገብ እንደማያስፈልግ በመግለጽ፤ ወዲያውኑ ፎቶ አንስተው ትክክለኛ ያልሆነ መታወቂያን በመስራት የሚሰጡ አካላት መኖራቸው ተረጋግጧል።

ይህንን ሕገ-ወጥ ሥራ በሚሰሩ አካላት ላይ ክትትል በማድረግ እንዲሁም የሚቀርቡ ጥቆማዎችን መሠረት አድርጎ ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ እርምጃ እንዲወሰድባቸው እንደሚደረግም ተናግረዋል።

ከዚህ ባሻገር ግን ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መለያ ቁጥሩን ብቻ በመያዝ መገልገል እንደሚችሉ የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ዜጎች ግዴታ የታተመውን የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደማይጠበቅባቸው አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮናስ አለማየሁ በበኩላቸው፤ ከመታወቂያ ጋር ተያይዞ የሀሰተኛ ሰነድ ስርጭት አደገኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን በዚህ ረገድ ገና መሠራት የሚገባው ከፍተኛ ሥራ መኖሩን ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...