” ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናውን ሲጨርስ Finish and Submit ሳያደርግ መውጣት የለበትም “

Date:

አጠቃላይ 190 ሺህ ተፈታኞች ፈተናቸውን በኦንላይን ይወስዳሉ።

የመጀመሪያ ቀን የኦንላይን ፈተና ውሎን ተከትሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

በዚህም ፤ ” ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናውን ሲጨርስ Finish and Submit ሳያደርግ መውጣት የለበትም ” ብሏል።

” ተፈታኙ ይህንን ማድረጉንም በፈተና ክፍሉ የተመደበ ባለሙያ ማረጋገጫ ሳይሰጠው እና ተፈታኙም ፈተናውን መጨረሱን በፊርማው ሳያረጋግጥ ከመፈተኛ ክፍል መውጣት አይኖርበትም ” ሲል አሳስቧል።

ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍል እንደገቡ ማሳወቅ እና ለዚህ ጉዳይ ተባባሪ ሆኖ ካልተገኙም በፈተና ማስፈጸሚያ ፕሮቶኮል መሰረት ተገቢው የእርምት ወይም አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ አዟል።

ሌላው ሚኒስቴሩ ፥ በተለያየ ምክንያት ” ሲስተም ዘጋብን ” በማለት ፈተና ክፍል ውስጥ የሚቀመጡ ተፈታኞችን በተለያዩ መንገዶች የማጣራት ሥራ በመስራት አስፈለጊውን የእርምት ወይም አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰድ እንደሚኖርበትም አሳስቧል።

ለምሳሌ፦ ስንተኛ ጥያቄ ላይ እንዳለ ወይም እንደዘጋበት / ባት መጠየቅ እና የተሰጠው መልስ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር የሚጣረስ ሆኖ ከተገኘ በፈተና ማስፈጸሚያ ፕሮቶኮል መሰረት ተገቢውን እርምጃ እንዲወሰድ ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...