የልጅ ተመስገን መለሰ “ኢቲዲኤም ቢትስ” የሙዚቃ አልበም ዛሬ ጥር 8 ከምሽቱ 12:00 ላይ እንደሚለቀቅ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ሀዘን ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንደተራዘመ አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ አስታውቀዋል።
አዘጋጆቹ ተከታዩን መልዕክት አስተላልፏል”በአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት ምክንያት ጥልቅ ሀዘን ስለተሰማን ዛሬ ማታ ጥር 8 ሊለቀቅ የነበረው የETDM Beats የልጅ ተመስገን መለሰ አልበም ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን በትህትና እናሳውቃለን። ለቤተሰቡ እና ለመላው አድናቂዎቹ መፀናናትን እንመኛለን”።
