በሀገራችን የሚሰበሰበው የደም መጠን ከህዝቡ ቁጥር አንፃር አነስተኛ ነው ተባለ

Date:

የኢትዮጵያ የደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት በደም ፍላጎትና አቅርቦት መካከል ክፍተት መኖሩን ገልጹዋል፡፡

ይህን የአቅርቦት እና የፍላጎት አለመጣጣም ችግርን ለማስተካከል የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እና የእምነት ተቋማት ትልቅ ሚና እንዳላቸው የኢትዮጵያ ደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ታዬ ተናግረዋል።

በቂ የደም አቅርቦት እንዲኖር እና የደም ህክምና የሚፈልጉ ታካሚዎችን ህይወት ለመታደግ አሁንም ጥረቶች እየተደረጉ እዳሉ የገለጹ አቶ ሃታሙ በፍላጎት እና አቅርቦት መካከል አሁንም ክፍተት መኖሩን አስታውቋል።

በ2017 በጀት አመት 8 ወር ፤ለመሰብሰብ ከታቀደው 3 መቶ 42ሺ ዮኒት ደም ውስጥ 2 መቶ 75ሺ 2 መቶ 86 ዮኒት ደም ማሰባሰብ መቻሉን አንስተዋል ፡፡ ይህም ከታቀደው 80 በመቶ ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በኦርቶዶክስ እና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የፆም ወቅት በመሆኑ የደም እጥረት እንዳይከሰት ስራዎች እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...