በሀገራችን የሚሰበሰበው የደም መጠን ከህዝቡ ቁጥር አንፃር አነስተኛ ነው ተባለ

Date:

የኢትዮጵያ የደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት በደም ፍላጎትና አቅርቦት መካከል ክፍተት መኖሩን ገልጹዋል፡፡

ይህን የአቅርቦት እና የፍላጎት አለመጣጣም ችግርን ለማስተካከል የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እና የእምነት ተቋማት ትልቅ ሚና እንዳላቸው የኢትዮጵያ ደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ታዬ ተናግረዋል።

በቂ የደም አቅርቦት እንዲኖር እና የደም ህክምና የሚፈልጉ ታካሚዎችን ህይወት ለመታደግ አሁንም ጥረቶች እየተደረጉ እዳሉ የገለጹ አቶ ሃታሙ በፍላጎት እና አቅርቦት መካከል አሁንም ክፍተት መኖሩን አስታውቋል።

በ2017 በጀት አመት 8 ወር ፤ለመሰብሰብ ከታቀደው 3 መቶ 42ሺ ዮኒት ደም ውስጥ 2 መቶ 75ሺ 2 መቶ 86 ዮኒት ደም ማሰባሰብ መቻሉን አንስተዋል ፡፡ ይህም ከታቀደው 80 በመቶ ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በኦርቶዶክስ እና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የፆም ወቅት በመሆኑ የደም እጥረት እንዳይከሰት ስራዎች እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...