በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

Date:

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1 ሺህ 655 ኢትዮጵያውያን መካከል የመጀመሪያዎቹ 320 ተመላሾች አዲስ አበባ ገብተዋል።

በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ይህ ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት በሪያድ የሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሚሲዮን እና በጂዳ የሚገኘው ቆንስላ ጽሕፈት ቤት በቅንጅት ባከናወኑት ጥረት የተመዘገበ መሆኑ ተገልጿል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞም መንግሥት ኅብረተሰቡ በሕገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች የሐሰት የማህበራዊ ሚዲያ ማታለያዎች ሳይደለል ከሕገወጥ የውጭ ሀገር ጉዞ ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል።

ዜጎችን ለከፍተኛ ችግር የሚዳርጉ ሕገወጥ ደላሎችን በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ የተጀመሩት የተቀናጁ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መረጃ አረጋግጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

አሜሪካ እና እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ለአገሪቱ ጦር የማስረከብ ዕቅድ

አሜሪካ ድጋፏን በሰጠችው ዕቅድ መሠረት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የደቡብ...