በሶማሊያው ፕረዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ ላይ የቦምብ ጥቃት ደረሰባቸው

Date:

ሁለት ከፍተኛ የመንግስት እና ወታደራዊ ባለስልጣናት ለሮይተርስ እንዳረጋገጡት ፕረዚዳንቱ ጥቃቱን ተከትሎ ደህና መሆናቸውን  ገልጸዋል።

ጥቃቱን የተመለከቱ ወታደሮች እና የአካባቢው ነዋሪዎች የፕረዚዳንቱ ኮንቮይ መምታቱን አረጋግጠዋል።  የሮይተርስ ጋዜጠኛ በቦታው በተገኘበት ሰዓትም በፕረዚዳንቱ ቤተ መንግስት አካባቢ በደረሰው ጥቃት የአራት ሰዎች አስከሬንን መመልከት ችሏል።

አልሸባብ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ባለው የቴሌግራም ቻናል ላይ ባሰፈረው መግለጫ “የእኛ ተዋጊዎቻችን ሀሰን ሼክ መሀመድን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ከፕሬዚዳንት ቤተ መንግስት ለቀው ወደ አየር ማረፊያ ሲሄዱ ኢላማ አድርገናቸዋል” ይላል።

የሶማሊያ መንግስት ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕረዚዳንቱ ግን ሰላም መሆናቸውንና በጉዟቸውም አልሸባብን እየተዋጋበት በሚገኘው በመካከለኛው ሸበሌ አደን ያባል ግዛት ካሉ ወታደሮችን ጋር አቦሮ ለማፍጠር እንደነበርና በቦታውም እንደተገኙ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...