በሸገር ሬዲዮ ጋዜጠኛ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለመስከረም 14 ቀን ተቀጠረ

Date:

የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ፣ ጋዜጠኞቹን በቁጥጥሩ ስር ካደረገ በኋላ ለ2ኛ ጊዜ ተጨማሪ የምርመራ ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢያመለክትም ጉዳዩን ያየው የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በ50,000 ብር ዋስትና እንዲለቀቁ መስከረም 7/2018 ዓ.ም ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወሳል፡፡

በውሳኔው ቅር የተሰኘው ፖሊስ በይግባኝ ለጠቅላይ ፍ/ቤት አመልክቷል፡፡

የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት 2ኛ የወንጀል ይግባኝ  ችሎት ፣ ዛሬ በዋለው ችሎቱ ፣ የፌዴራል ፖሊስና የጋዜጠኞቹን ጠበቃ አቤቱታ ካዳመጠ በኋላ ውሳኔ ለመስጠት ለመስከረም 14 ቀን 2018 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

የሸገር ሬዲዮ ጋዜጠኞች ትዕግስት ዘሪሁን እና ምንታምር ፀጋው በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ዛሬ 20ኛ ቀናቸው ነው፡፡

📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...