ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

Date:

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ በ1.9 ቢሊዮን ብር የገነባውን ሆቴል በይፋ ሥራ ጀምሯል።

ሻለቃ ኃይሌ በምርቃቱ ላይ ባደረገው የምስጋና ንግግር፣ ደብረ ብርሃን የኢንዱስትሪ፣ የሥራ እና የጽናት ከተማ መሆኗን ጠቅሶ፤ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት በመብቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ደስታ ገልጿል።

አክሎም “እኛ ኢንቨስት ስናደርግ ትልቁ ዓላማችን የሥራ ዕድል መፍጠርና የአገራችንን ገጽታ መገንባት ነው” ብሏል።

ሆቴሉ ሲገነባ የነበሩ ፈተናዎችን በከተማዋ አስተዳደርና በሕዝቡ ድጋፍ ማለፍ እንደተቻለ የገለጸው ሻለቃ ኃይሌ፤ “ ‘አይቻልም’ የሚል ቃል በኢትዮጵያዊያን መዝገበ ቃላት ውስጥ መኖር የለበትም፤ በትጋትና በሥራ ካሰብንበት እንደርሳለን” ሲል የሥራን አስፈላጊነት አጽንኦት ሰጥቷል።

ይህ አዲስ የተመረቀው ሆቴል ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የቱሪዝም መዳረሻ እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን፣ ማህበረሰቡም ይህን ታላቅ ሀብት እንዲንከባከበው ጥሪ ቀርቧል።

ሻለቃ ኃይሌ ለፕሮጀክቱ መሳካት ድጋፍ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናውን አቅርቧል።

ይህ 11ኛው የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ፕሮጀክት ለአካባቢው ነዋሪዎች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርና ለከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልፁል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...