በታቦተ ህግ ላይ በመሳለቅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክብር የሚነካ ቪዲዮ ያሰራጨ ግለሰብ በእስር ተቀጣ

Date:

የጥምቀትን በዓልን ምክንያት በማድረግ በታቦተ ህግ ላይ በመሳለቅ በቲክቶክ ያሰራጨ ግለሰብ በ1 ዓመት ከ4 ወር ቀላል እስር እንዲቀጣ መወሰኑን የወላይታ ዞን አረካ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

ፖሊስ እንደገለፀው ወንጀሉን ከፈፀሙ ግለሰቦች መካከል በቀን 25/05/2017 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውሎ በህግ ጥላ ስር የቆየው ወጣት አቤል አዳፍሬ ነዋሪነቱ በአረካ ከተማ አረዳ ቀበሌ አስተዳደር ውስጥ ሲሆን በማህበራዊ ትስስር ገፅ ለተከታዮቹ ባጋራው የቲክቶክ ቪዲዮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክብር የሚነካ የእምነቱ ተከታዮችንም ያስቆጣ ተግባር መፈጸሙ ተገልፆአል።

ፖሊስ የተከሳሹን የምርመራ ሂደቱን ጨርሶ ወደ አቃቤ ህግ በማስተላለፍ አቃቤ ህግ በመሰረተው ክስ ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ህግ ጥፋተኛ በመሆኑ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው ፍርድ ቤት በተከሳሹ ላይ ያስተምራል ያለውን በ 1 አመት ከ 4 ወር ቀላል እሥራት እንዲቀጣ መወሰኑን የዘገበው የከተማዋ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...