በታቦተ ህግ ላይ በመሳለቅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክብር የሚነካ ቪዲዮ ያሰራጨ ግለሰብ በእስር ተቀጣ

Date:

የጥምቀትን በዓልን ምክንያት በማድረግ በታቦተ ህግ ላይ በመሳለቅ በቲክቶክ ያሰራጨ ግለሰብ በ1 ዓመት ከ4 ወር ቀላል እስር እንዲቀጣ መወሰኑን የወላይታ ዞን አረካ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

ፖሊስ እንደገለፀው ወንጀሉን ከፈፀሙ ግለሰቦች መካከል በቀን 25/05/2017 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውሎ በህግ ጥላ ስር የቆየው ወጣት አቤል አዳፍሬ ነዋሪነቱ በአረካ ከተማ አረዳ ቀበሌ አስተዳደር ውስጥ ሲሆን በማህበራዊ ትስስር ገፅ ለተከታዮቹ ባጋራው የቲክቶክ ቪዲዮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክብር የሚነካ የእምነቱ ተከታዮችንም ያስቆጣ ተግባር መፈጸሙ ተገልፆአል።

ፖሊስ የተከሳሹን የምርመራ ሂደቱን ጨርሶ ወደ አቃቤ ህግ በማስተላለፍ አቃቤ ህግ በመሰረተው ክስ ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ህግ ጥፋተኛ በመሆኑ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው ፍርድ ቤት በተከሳሹ ላይ ያስተምራል ያለውን በ 1 አመት ከ 4 ወር ቀላል እሥራት እንዲቀጣ መወሰኑን የዘገበው የከተማዋ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...