በታቦተ ህግ ላይ በመሳለቅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክብር የሚነካ ቪዲዮ ያሰራጨ ግለሰብ በእስር ተቀጣ

Date:

የጥምቀትን በዓልን ምክንያት በማድረግ በታቦተ ህግ ላይ በመሳለቅ በቲክቶክ ያሰራጨ ግለሰብ በ1 ዓመት ከ4 ወር ቀላል እስር እንዲቀጣ መወሰኑን የወላይታ ዞን አረካ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

ፖሊስ እንደገለፀው ወንጀሉን ከፈፀሙ ግለሰቦች መካከል በቀን 25/05/2017 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውሎ በህግ ጥላ ስር የቆየው ወጣት አቤል አዳፍሬ ነዋሪነቱ በአረካ ከተማ አረዳ ቀበሌ አስተዳደር ውስጥ ሲሆን በማህበራዊ ትስስር ገፅ ለተከታዮቹ ባጋራው የቲክቶክ ቪዲዮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክብር የሚነካ የእምነቱ ተከታዮችንም ያስቆጣ ተግባር መፈጸሙ ተገልፆአል።

ፖሊስ የተከሳሹን የምርመራ ሂደቱን ጨርሶ ወደ አቃቤ ህግ በማስተላለፍ አቃቤ ህግ በመሰረተው ክስ ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ህግ ጥፋተኛ በመሆኑ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው ፍርድ ቤት በተከሳሹ ላይ ያስተምራል ያለውን በ 1 አመት ከ 4 ወር ቀላል እሥራት እንዲቀጣ መወሰኑን የዘገበው የከተማዋ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...

በኢትዮጵያ በካንሰር ከሚያዙ ሕፃናት መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ህክምና አያገኙም

በኢትዮጵያ በየዓመቱ በካንሰር ከሚጠቁ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ...