በቴሌ ብር 14 ቢሊዮን ብር  ለደንበኞች ብድር ሰጥቻለሁ

Date:

ዳሸን ባንክ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ግለሰብ ደንበኞች፣ ነጋዴዎች እንዲሁም ወኪሎች በቴሌብር የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ ባቀረበው አገልግሎት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 14 በሊዮን ብር ብድር መማቅረቡን አስታውቋል፡፡

መደበኛ የፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ላልሆነው የማህበረሰብ ክፍል መሻሻል ከፍተኛ ሚና ያላቸውን፣ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ የሞባይል አነስተኛ ብድር፣ የኦቨር ድራፍትና የቁጠባ አገልግሎቶች ዳሸን ባንክ በዚህ አገልግሎት እያቀረበ ነው፡፡

በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ2.3 ሚሊዮን በላይ የሚደርሱ ደንበኞች በቴሌብር አማካኝነት ከዳሸን ባንክ ከ8.4 ሚሊዮን በላይ መጠን ያላቸው የገንዘብ ዝውውሮችን (ትራንዛክሽኖችን) ፈፅመው 14 ቢሊዮን የሚደርስ ብድር እንደቀረበላቸው ባንኩ ያስታወቀው።

ዳሸን ባንክ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በአጋርነት የግለሰብ ደንበኞች፣ ነጋዴዎች እንዲሁም ወኪሎች “መላ” የተሰኘውን የአነስተኛ ብድር አገልግሎት፣ በቴሌብር በአካውንታቸው ላይ ያላቸው ቀሪ የሂሳብ መጠን በቂ ባልሆነበት ጊዜ የሚጠቀሙት “እንደኪሴ” የተሰኘ የክሬዲት ክፍያ(ኦቨርድራፍት) ብድር አገልግሎት እያቀረበ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም “ሳንዱቅ” የተሰኘ ደንበኞች ከወለድ ነጻ ወይም የተለያየ የወለድ መጠን የሚታሰብባቸው የቁጠባ አይነቶች በዚህ አገልግሎት መቅረቡን ባንኩ አስታውቋል፡፡

KGEthiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እስከ አምስት ዓመት እስራት የሚያስቀጡ የመረጃ ነጻነት አዋጅ ጸደቀ

ለ15 ዓመታት በስራ ላይ ከቆየው “የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት...

በደቡብ አፍሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተላለፈ ማስጠንቀቂያ

በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እየተከታተለና...

በበጀት አመቱ 22.9 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ እየተሠራ ነው

ከታቀደው 22 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ኩንታል እስካሁን  20...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...