በአዲስ አበባ 35 ሺሕ መምህራን በልዩ መታወቂያ የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኙ መሆኑ ተገለጸ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ 35 ሺሕ መምህራን በልዩ መታወቂያ ከክፍያ ነፃ የሆነ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጣቸው መሆኑን የአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አካሉ አሰፉ እንደገለጹት፤ በቀደመው በጀት ለአንድ መምህር በቀን 16 ብር ተመድቦ የትራንስፓርት አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል።

ይህ በጀት በአሁኑ ወቅት ወደ አንድ ቦታ ለመድረስ እንኳን የማይበቃ ሊሆን እንደሚችል የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ወጪው ከተመደበው በጀት ጋር የማይጣጣም መሆኑን ጠቁመዋል።

መምህራን የሕዝብ አገልጋይና ዜጋን የመገንባትና የማነፅ ሚና ያላቸው በመሆኑ፤ ልዩ መታወቂያው ከክፍያ ነፃ የትራንስፓርት አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ገልጸዋል።

በዚህም “መምህራንን ተጠቃሚ ማድረግ ልጆቻቸውን ማስተማር የማይችሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ ማድረግ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል” ሲሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩም ይሄን ታሳቢ በማድረግ ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...

በኢትዮጵያ በካንሰር ከሚያዙ ሕፃናት መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ህክምና አያገኙም

በኢትዮጵያ በየዓመቱ በካንሰር ከሚጠቁ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ...